ራምቦል
ራምቦል እ.ኤ.አ በ1945 የተመሰረተ ዘርፈ ብዙ ሙያ ባለቤት የሆነ መሪ የምህንድስና፣የንድፍ እና የማማከር ድርጅት ነው፡፡ ኩባንያው በመላው አለም ከ15,500 በላይ ሙያተኞችን ቀጥሮ ያሰራል፡፡ በ35 ሀገራት ውስጥ በሚገኙ 300 ቢሮዎቹ ራምቦል የሀገር ውስጥ ተሞክሮውን ከአለም አቀፍ መነሻ እውቀት ጋር በማጣመር በደንበኞቻችን፣ የመጨረሻ ተጠቃሚዎች እና በአጠቃላይ ማህበረሰብ ላይ እውነተኛ ልዩነት የሚፈጥሩ መፍትሄዎችን ለማግኘት በትጋት ይጥራል፡፡ ራምቦል በዓለም ዙሪያ ላሉት ከተሞች በርካታ የትራንስፖርት ማስተር ፕላኖችን አዘጋጅቷል፡፡ የኤስሲቲዲፒ ፕሮጀክትን ከማስተዳደር በተጨማሪም የትራንስፖርት ዕቅድ ዝግጅት እና ሞዴል ዝግጅት ሙያተኞቻችን፣ የባለ ድርሻ አካላት፣ የስታስቲክስ ሙያተኞች፣ የትራፊክ መሀንዲስ፣ የህዝብ ትራንስፖርት እና የጭነት ትራንስፖርት እቅድ ሰራተኞች ሁሉም በየሙያ መስካቸው ለስራው መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ናቸው፡፡
ሞባይሊቲ ኢን ቼይን
ኤምአይሲ እ.ኤ.አ በ2009 የተመሰረተ አለም አቀፍ የትራንስፖርት እቅድ አውጪ ድርጅት ነው፡፡ ኤምአይሲ የስራ ቦታዎቹ በሚላን፣ ሞስኮ እና ኒው ዮርክ የሚገኙ ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ከዩናይትድ ስቴትስ እስከ ቻይና እና ከአውሮፓ አስከ አፍሪካ ድረስ በተለያዩ ስራዎች ላይ ይሰማራል፡፡ ኤምአይሲ በእውነቱ የተመሰረተው ተንቀሳቃሽነት በአኗኗራችን እና በህይወታችን ጥራት ላይ ተጽዕኖ ስለሚያሳድር እና የምንንቀሳቀስበትን አቅጣጫ በጥልቀት በመረዳት የእለት ተዕለት ልምዶችን የማሻሻል ምኞት ነው የተፈጠረው። እነዚህን ፈታኝ ግቦች ለማሳካት እና ለመላው የአለም ህዝብ ዘላቂነት ያለው ሰብዓዊ ማህበረሰብ እድገትን ለማምጣት ኤምአይሲ አዳዲስ ነገሮችን ለማመንጨት ሁልጊዜም ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነው፤ በአዳዲስ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎች ብቻ ሳይሆን በማንኛውም ጊዜ በማያቋርጥ ማሻሻያ እና ምርምር የሚዘልቁ ናቸው፤ ነገር ግን እንዲሁም ምስጋና ይግባውና መተላለፊያው፣ ንቁ ተንቀሳቃሽነት እና ለእግር ጉዞ ምቹነት እና የሰው ልኬት አቀራረብ ለቦታው ፍሬያማነት የወደፊት ዘላቂነትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ ሚና ይጫወታሉ። ኤምአይሲ የኤስሲቲዲፒ ፕሮ ክትን ከትራንስፖርት ፕላን ዝግጅት እና ጂአይኤስ ኤክስፐርቶች ጋር በመተባበር ይደግፋል::
አይአርዲ ኢንጂነሪንግ
አይአርዲ በጣሊያን የተመሰረተ አለም አቀፍ የምህንድስና አማካሪ ድርጅት ሲሆን በመላው አለም ለመንገድ፣ የባቡር መንገድ፣ ድልድዮች፣ አውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የህንጻ አገልግሎት መስጫዎች፣ የውሃ እና የሀይል መሰረተ ልማቶች፣ አዳዲስ አጠቃላይ መፍትሔዎችን ያቀርባል፡፡ አይአርዲ በፕሮጀክቱ አጠቃላይ የትግበራ ዙር ለመንግስት እና ለግሉ ዘርፍ ደንበኞች የዲዛይን፣ ቁጥጥር፣ የቴክኒክ እገዛ እና ግዢ (ዲዛይን እና ግንባታ፣ ቢኦቲ፣ ፒፒፒ፣ ስምምነት፣ ወዘተ) የፕላን ዝግጅት እና የቴክኒክ አዋጭነት የምጣኔ ሃብታዊ – የገንዘብ ጥናቶች የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ያቀርባል፡፡ አይአርዲ በህዝብ ትራንስፖርት፣ የትራንስፖርት እቅድ ዝግጅት፣ የምጣኔ ሃብታዊ እና የገንዘብ ሙያዊ ትንተናዎች አማካኝነት ለኤስሲቲዲፒ ፕሮጀክት አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡
ኤምጂኤም ኮንሰልት
ኤምጂኤም ኮንሰልት በአጠቃላይ የሲቪል ምህንድስና ስራዎች ላይ ሙያዊ አገልግሎቶችን የሚቀርብ መሪ የኢትዮጵያ አማካሪ ድርጅት ነው፡፡ ኤምጂኤም ለመንግስት እና ለግሉ ዘርፍ ደንበኞች በመንገድ እና ድልድይ ዲዛይን እና ምህንድስና እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ላይ እንደ ህንጻ ግንባታ ባሉ ስራዎች ላይ ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ኤምጂኤም ለኤስሲቲዲፒ ፕሮጀክት በትራንስፖርት ምህንድስና/የትራንስፖርት እቅድ ዝግጅት ግራፊክስ እና ድረ ገጽ ዲዛይን እንዲሁም በሙያዊ የትርጉም አገልግሎቶች ላይ በሀገር ውስጥ ሙያዊ ልምዱ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡